የአዳሪ አብነት ት/ቤቱ የስኬት ምዕራፎች
የአዳሪ አብነት ት/ቤቱ የስኬት ምዕራፎች
ከተመሠረተበት 2006 ዓ.ም ጀምሮ በ10 ተማሪዎች ሥራውን የጀመረው አዳሪ አብነት ት/ቤቱ አሁን ላይ በተለያየ ዕድሜና የትምህርት ደረጃ የሚገኙ ከ 150 በላይ ተማሪዎችን አቅፎ ይገኛል።
ለአብነት ትምህርት መስጫነት የሚያገለግሉ የቁጥር/ንባብ ፣ የዜማ ፣ የቅኔ ፣ የቅዳሴ ፣ የአቋቋም ፣ የትርጓሜ ፣ የስብከት ወንጌል እና የበገና ትምህርቶች የሚሰጡባቸው ስምንት (8) ጉባኤ ቤቶች በዘመናዊ መልክ ተገንብትዋል። እኚህም ጉባኤ ቤቶች፦
፩. የቁጥር እና ንባብ ጉባኤ ቤት
፪. የዜማ ጉባኤ ቤት
፫. የቅዳሴ ጉባኤ ቤት
፬. የቅኔ ጉባኤ ቤት
፭. የአቋቋም ጉባኤ ቤት
፮. የትርጓሜ ጉባኤ ቤት
፯. የስብከተ ወንጌል ጉባኤ ቤት
፰. የበገና ጉባኤ ቤት
በቤተክርስቲያኒቱ እና አዳሪ የአብነት ት/ቤቱ
ተማሪዎችን ከታች ጀምሮ በማብቃት ለቅኔ እና አቋቋም ጉባኤ ቤት መጀመር ትልቅ ሥራ ሠርቷል ።
ደቀመዛሙርት ባላቸው ጊዜ ከአብነት ትምህርቱ ጎን ለጎን የበና ድርደራን ተምረው ራሳቸውንና ሌሎችንም የማረጋጋት ጸጋ እንዲኖራቸው እንዲሁም በቅዱስ ዳዊት ሀብት ቤተክርስቲያንን እንዲያገለግሉ የበገና ሥልጠና በመውሰድ ላይ ናቸው ።
የአብነት ት/ቤቱ ጥራቱን የጠበቀ ትምህርትን በማስተማር እስካሁን ድረስ ከ500 በላይ ተማሪዎችን የዲቁና ክህነት እና 15 ዲያቆናትን የቅስና ማዕረግ አስቀብሎ ወደ አገልግሎት አሰማርቷል።
